tg-me.com/EthioHumanity/7143
Last Update:
🌗በአንድ ወቅት ጫካ ውስጥ መውለጃዋ የቀረበ አንዲት ሚዳቆ የመውለጃ ሰዐቷ ደርሶ ትግል ላይ ሳለች ድንገት አከባቢዋን ስትቃኝ ከፊት ለፊቷ ወንዝ ፣ ከኋላዋ ቀስት ያነጣጠረባትን አዳኝ፣ ወደ ጎን ስትዞር የተራበ አንበሳ አሰፍስፎባት ትመለከታለች።
ይህም ሳይበቃት ጭማሪ ከፍተኛ ነጎድጓድና መብረቅ ያጀበው ደመና መጥቶ ሰማዩን ያጨልመዋል። መብረቁም ሀይለኛ ስለነበር ደኑን ይመታውና ከፍተኛ ቃጠሎን ያስነሳባታል። ምን ታድርግ?
ወደ ፊት ሮጣ እንዳታመልጥ ጥልቅ ወንዝ ተደቀነባት፤ከኋላዋ አዳኙ፤ከጎኗ ደግሞ አንበሳው፤ወደ ጫካ ገብታ እንኳ እንዳትደበቅ ደኑ ከፍተኛ ቃጠሎ ላይ ነው...
በዚያ ላይ የውልደት ህመም ነፍስ ውጪ ግቢ እያስባላት ነው ...
💡ሚዳቆዋ በዚህ ውጥረት ውስጥ ሆና ትኩረቷን መፈፀም ወደ ምትችለው ነገር ላይ ብቻ በማድረግ ቀሪውን ለፈጣሪ በመተው በመወለድ ላይ ስላለው ልጇ ብቻ ማሰብ ጀመረች.....
አዳኙ ቀስቱን አነጣጥሮ ሊለቅ ባለበት ቅፅበት ድንገት የመብረቁ ብልጭታ አይኑ ላይ ብዥታ ፈጠረበትና ቀስቱ ተስፈንጥሮ ወደ ተራበው አንበሳ ይሄድና አንበሳውን ይገለዋል።
አጉበድብዶ የነበረው ደመናውም መዝነብ ይጀምርና የደኑን ቃጠሎ በቅፅበት አጠፋው። በጭንቅ ታጅባ የነበረችው ሚዳቆም በሰላም ተገላገለችና ወደ ቀደመው ህይወቷ ተመለሰች።
🔑አንዳንዴ በህይወትህ ውስጥ በብዙ ፈተናዎችና ጭንቀቶች ልትከበብ ትችላለህ፣ ያኔ አንተ ልትፈታው በምትችለው ነገር ላይ ብቻ አትኩርና ቀሪውን ለመፍትሄዎች ሁሉ ባለቤት ለሆነው ለፈጣሪህ ተወው።
መውጫ መፍትሄ አንተጋ እንጂ ፈጣሪህ ዘንድ አይጠፋም። አስታውስ ሁሌም ትላልቅ ወይም ከባባድ ፈተናዎች አሉብኝ ብለህ ለፈተናዎች እውቅና ከመስጠትህ ይልቅ የከባባድ ፈተናዎች አለቃ የሆነው ፈጣሪ አለኝ እያልክ ጭንቀቶችህን አቅልላቸው፣ሁሌም በፈጣሪህ ፈፅሞ ተስፋ አትቁረጥ!!!
📍ገጣሚ በረከት በላይነህ ''ሳይፀልዩ ማደር'' በምትለው ውብ ግጥሙ እንለያይ፣
''ሳይፀልዩ ማደር''
የተራበ ነብር ከሩቅ ተመልክታ
ሚዳቋ ፀለየች....
"አውጣኝ አውጣኝ" አለች ለፈጠራት ጌታ
...
ነብሩም ተርቦ
ወደ አምላኩ ቀርቦ
ሚዳቆዋን አይቶ - አንጀቱ ከሆዱ እንደተጣበቀ
ፈቅዶ እንዲሰጠው - አምላኩን ጠየቀ
...
የሁላችን ሰሪ
ፀሎታቸውንም ሰማቸው ፈጣሪ
አምላክም በድምፁ ሚዳቆዋን አላት
"እሩጠሽ አምልጪ ከበረታው ጠላት"
...
ነብሩንም አለው - "እሩጥ ተከተላት ምግብ አድርገህ ብላት"
ሚዳቆዋ ስትሮጥ
ከነብር ለማምለጥ
ነብሩም ሲከተላት
ሆዱን ሊሞላባት
.
ቋጥኙን ስትዘል እግሯ ተስፈንጥሮ
ሆዱን ብትረግጠው የተኛው ከርከሮ
ከእንቅልፉ ሲነቃ ልክ ሲደነብር
ጉሮሮውን ያዘው የፀለየው ነብር
...
አውጣኝ ያለው ወቶ አብላኝ ያለው በላ
ሳይፀልይ ያደረው ከርከሮ ተበላ
ውብ አሁን ❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
BY ስብዕናችን #Humanity
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/EthioHumanity/7143